ይህ ለኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተዘጋጀ ማህበረሰባዊ የውውይት መድረክ ነው። በመድረኩ ገብቶ ለመሳተፍ ምዝገባ በመፈፀም የግል መግቢያ ቁልፍ ያድርጉ (ዩዘር ኔም እና ፓስዎርድ)። መድረኩ ሁለት ዓይነት ይዘት አለው። አንደኛው፤ እንደግለሰብ የተለያዩ የጠንካራ ስብዕና ዓይነቶችን ለመገንባት ወይም ለማጎልበት የሚረዳን የውይይት መድረክ ነው። የተለያዩ ዕሴቶችን፣ የከፍተኛ የሞራልና ሥነምግባር ልዕልና መሠረቶችን፣ የኑሮ ዓላማ ዕቅድን የማውጣትና መሥራት ዘዴዎችን፣ የገንዘብ ወይም ሃብት አያያዝ ብቃትንና አካሄድን የምንማማርበት የጋራ ማህበራዊ መድረክ ነው። ሁለተኛው፥ በየምንኖርበት አካባቢ የሚገጥሙንን ግለሰባዊ የኑሮ ወይም ህይወት ተግዳሮቶች በተግባር የተረጋገጡ መፍትሔዎችን ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ መንገዶችን ተጉዘው በስኬት መፍትሄውን ከሚያውቁ ወገኖች ለመስማት የምንጠቀምበት መድረክ ነው። *** This platform loves to give huge credit to the authors and book cited hereby, but also offer our sincere gratitude for they were our basic sources for most of Forum 1 content. Authors Christopher Peterson and Martin Seligman wrote this wonderful book: "Character Strengths and Virtues: A Handbook and Classification." The platform adopted, added to it, and augmented their work to better fit our unique Ethiopian society. The platform highly encourages all visitors to read their extensively researched, instructional and powerfully transformative book. ***

We have 2 Forum discussion boards for the community.

የውይይት መድረክ ቁጥር አንድ፥ ቁልፍ ግለሰባዊ የዕሴትና ቀናዊ ሥነ ባህርያት ዕድገትን አጎልባች ማህበረሰባዊ የውይይት መድረክ ። (Forum 1: To Discuss Key Personal Character Development Values within the Community.)

የውይይት መድረክ ቁጥር ሁለት፥ በመላው ዓለም ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን አካባቢያዊና ግለሰባዊ የኑሮ ፈተናዎችን በጋራ ለመቅረፍ የሚረዳ ማህበረሰባዊ የውይይት መድረክ ። (Forum 2: To Discuss Community Suggested Solutions for Local Life Challenges of Individual Ethiopians Living Around the World.)

የተዘጋጀው ለማን ነው?

ይህ ማህበረሠባዊ የፕሮጀክታችን ክፍል  ዕድሜ፣ ጾታ፣ ጎሳ፣ ሃይማኖት፣ ማህበረሰብ፣ ሥፍራ፣ እና የመሳሰሉት ሰብዓዊ መገለጫዎችን ሳይለይ ከታች እንደተጠቀመጠው በ9 ክፍለዓለማት በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን የሚያሣትፍ የጋራ መድረክ ነው ፡፡

የዚህ መድረክ ዓላማዎች ምንድን ናቸው?

የዚህ መድረክ ዓላማ የሚከተሉት ሁሉ ናቸው። ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በግለሰብ ደረጃም ሆነ እንደ ማህበረሰብ በየአሉበት በኑሮአቸው እንዲደጋገፉ ለማድረግ። በወገናዊና አለኝታዊ ፍቅር፣ በቀና የትብብር መንፈስ ለመቀናጀት። እንዲሁም ሕዝባዊ ዕድገት ላይ ያተኮረ አዲስ የመረዳጃ ማህበራዊ መድረክን እንደ ባሕላዊ ተቋም አድርጎ ለመፍጠርም ነው።በዚህም መሠረት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ግለሰባዊ የኑሮ ጥራት ደረጃን ለማግኘት እንድንችል፣ እርስ በእራሳችን በመተጋገዝ በብቃት እያንዳንዳችን ወደምንፈልገው ከፍተኛ የኑሮ ጥራት  አቅጣጫና ደረጃ ከፍ ለመደራረግ፣ ቋሚ የማህበራዊ ትስስር ግንኙነት እንደ ብረት ሠንሠለት ተያይዞ የሚኖር መረብ መሆን እንዲችል። በበጎና ነፃ ትብብር ላይ ተመሥርቶ ተዛማጅ የሆነ ባህላዊ ዕሳቤና ተቋም በየአለንበት ለመፍጠር። የራሳችን ወገን ዓለም አቀፋዊ ጥራትና ብቃት ይዞ በዓለማችን የትም ስለሚገኝ አንዱ ለሌላው ወገኑ የዕውቀት፣ የልምድና የብቃት ኃይል ምንጭ እንዲሆንና እንዲያጎለብተው አመቺ መንገድ በመፍጠር በከፍተኛ ኢትዮጵያዊ አንድነት ስሜት ተነሳስተን ኑሮአችንን በየአለንበት እንድናሻሻል ይረዳ ዘንድ ነው። ዓላማችን እነዚህ ብቻ ናቸው። 

ከተሳታፊዎች ምን ይጠበቃል?

ሁላችንም ተሳታፊዎች በተወዳጁ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ መልካም ሥነምግባር፣ ፈርሀ እግዚአብሔር፣ የሕሊና ተገዢነት፣ ሀቀኝነት፣ ክብር፣ የወገናዊ ተቆርቋሪነት፣ ጥበበኛነት፣ በነፃ ብሔራዊ የትብብር አገልግሎትን የመስጠት መንፈስ ተሞልተን እና በፕሮጀክቱ ከፍተኛ ዓላማ እንዲሁም ጥቅም በማመን መሣተፍን ይጠበቅብናል።
ኢትዮጵያዊ አንድነት ፍቅርና ዕድገት ለዘላለም ይለምልም!!!